የሀገር ውስጥ ዜና

የኔዘርላንድስ ኩባንያ በኢትዮጵያ የሚገኙ የእንስሳት ባለሃብቶችን እንደሚደግፍ አስታወቀ

By Feven Bishaw

February 25, 2022

አዲስ አበባ፣የካቲት 18፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኔዘርላንድስ ኩባንያ የእንስሳት ሀብት ልማት ፕሮጀክት በመጀመር በኢትዮጵያ የሚገኙ የእንስሳት ባለሃብቶችን እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡

አምባሳደር ሂሩት ዘመነ በትላንተናው ዕለት በዓለም ከ40 አገራት በላይ የሚንቀሳቀስውንና ፒኮሊን/ ሺፕፐርስ የተሰኘውን የኔዘርላንድስ ኩባንያ የንግድ ዳይሬክተር ሚስተር ጄሮን ቤይጀርን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው በአዲሱ የእንስሳት ፕሮጅክት ዙሪያ አነጋግረዋቸዋል፡፡