አዲስ አበባ፣የካቲት 18፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኔዘርላንድስ ኩባንያ የእንስሳት ሀብት ልማት ፕሮጀክት በመጀመር በኢትዮጵያ የሚገኙ የእንስሳት ባለሃብቶችን እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡
አምባሳደር ሂሩት ዘመነ በትላንተናው ዕለት በዓለም ከ40 አገራት በላይ የሚንቀሳቀስውንና ፒኮሊን/ ሺፕፐርስ የተሰኘውን የኔዘርላንድስ ኩባንያ የንግድ ዳይሬክተር ሚስተር ጄሮን ቤይጀርን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው በአዲሱ የእንስሳት ፕሮጅክት ዙሪያ አነጋግረዋቸዋል፡፡