የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በመሰረተ ልማት ለማስተሳሰር እየሰራች ነው- አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ

By Tibebu Kebede

October 18, 2019

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በመሰረተ ልማት ለማስተሳሰር በሚደረገው ጥረት ተግታ እየሰራች እንደምትገኝ አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ ገለፁ።

በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ የሚመራ የኢትዮጵያ ፓርላማ ልዕካን ቡድን ጥቅምት 4 እና 5 2012 ዓ.ም በቤልጄም ብራሰልስ በተካሄደው የአፍሪካ ካርቢያን፣ ፓስፊክ እና የአውሮፓ ህብርት ፓርላማ ጥምር ጉባኤ ላይ ተሳትፏል።