አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በመሰረተ ልማት ለማስተሳሰር በሚደረገው ጥረት ተግታ እየሰራች እንደምትገኝ አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ ገለፁ።
በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ የሚመራ የኢትዮጵያ ፓርላማ ልዕካን ቡድን ጥቅምት 4 እና 5 2012 ዓ.ም በቤልጄም ብራሰልስ በተካሄደው የአፍሪካ ካርቢያን፣ ፓስፊክ እና የአውሮፓ ህብርት ፓርላማ ጥምር ጉባኤ ላይ ተሳትፏል።