አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአምቦ ከተማ በዛሬው ዕለት በተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ላይ በደረሰ የቦምብ ጥቃት በ29 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን ፓሊስ አስታወቀ።
የኦሮሚያ ፓሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አራርሳ መርደሳ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፥ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድና ለለውጥ አመራሩ በተካሄደ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት 29 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።