አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከታላቁ የአድዋ ድል የሃገሪቱ ፖለቲካና ፖለቲከኞች ትምህርት ሊወስዱ እንደሚገባ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ ፖለቲከኞች ተናገሩ ፡፡
የትግራይ ዴሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር አረጋዊ በርሄ እና የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ መጋቢ ብሉይ አብረሃም፥ ቀደምት አባቶችና እናቶች ስለ ሃገር አንድ ሆነው የከፈሉት መስዋእትነት ለታመመው ፖለቲካችን ማከሚያ እንደሚሆን አብራርተዋል ፡፡