የሀገር ውስጥ ዜና

የተለያዩ ኤምባሲዎች በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ዕረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

By Meseret Awoke

March 04, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ኤምባሲዎች አራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትረያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ዕረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ፡፡

በኢትዮጵያ የሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ በቅዱስነታቸው ዕረፍት ሃዘኑን ገልጾ ፥ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የማይተካ ሚና እንዳበረከቱ ገልጿል፡፡

በዚህም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

በሌላ በኩል በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ አራተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትረያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በማረፋቸው የተሰማውን ሃዘን ገልጿል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!