አበባ፣ የካቲት 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ብልፅግና ፓርቲ በብድር ስም የወጣው የፓርቲው ገንዘብ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከነ ወለዱ ታስቦ ተመላሽ እንዲደረግና ዝርዝር ሁኔታው ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በብድር ስም ገንዘብ የወሰዱ አመራርና ሰራተኞችም ከያዙት የመንግስትና የፓርቲ ኃላፊነት ከየካቲት 25/2014 ዓ.ም ጀምሮ እንዲነሱ መወሰኑን አስታወቀ።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ፓርቲው መግለጫ አውጥቷል።