Fana: At a Speed of Life!

44ኛው የካራማራ የድል በዓል በኢትዮ- ኩባ አደባባይ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን ምንም ልዩነት ሳይገድባቸው የሕይወትና የአካል መስዋዕትነት የከፈሉበት 44ኛው የካራ ማራ የድል በዓል በኢትዮ- ኩባ አደባባይ እየተከበረ ነው::

በበዓሉ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች፣ በጦርነት የተሳተፉ የወቅቱ የሠራዊት አባላት ዐርበኞች፣ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል::

የበዓሉን መርሃ ግብር÷ ኮረማሽ የጉዞ ማኅበር፣ የኢትዮጵያ እና የኩባ ሕዝቦች ወዳጅነት ማኅበር፣ የህጻናት አምባ ልጆች ከአዲስ አበባ ባህል ቱሪዝም እና ኪነጥበብ ቢሮ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው::

በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ባህል ቱሪዝም እና ኪነጥበብ ቢሮ የኪነ ጥበብ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰርፀ ፍሬስብሀት÷ ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነው በከፈሉት የህይወትና አካል መስዕዋትነት ወረራውን ቀልብሰው ድል ያደረጉበት ደማቅ ስፍራ የሚይዝ ታሪካችን ነው ብለዋል::

በዓሉ ለቱሪዝም ዘርፋ የሚኖረው ፋይዳ ከፍ ያለ በመሆኑ ወደፊት በስፋት እንደሚሰራበትም ጠቁመዋል::

ካራ ማራ ኢትዮጵያውያን ጀግኖች አባቶቻችን በአንድነት የዚያድባሬን የወረራ ህልም ያከሸፋበትና ድልን የተቀዳጁበት፣ ዳግም ዐድዋን እውን ያደረጉበት በመሆኑ÷ የዚህ ዘመን ትውልድ ደግሞ ሀገር ግንባታ ላይ ትኩረት አድርጎ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በመስራት የበለፀገች ኢትዮጵያን ለቀጣይ ትውልድ ማስረከብ ይኖርበታል ሲሉ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ የበዓሉ ተሳታፊዎች ገልፀዋል::

 

በአዲሱ ሙሉነህ
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.