Fana: At a Speed of Life!

በዐቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተበት ሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው በነጻ ተለቋል በሚል የሚናፈሰው ወሬ መሰረተቢስ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዐቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተበት ሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው በነጻ ተለቋል በሚል የሚናፈሰው ወሬ መሰረተ ቢስ መሆኑን የፍትሕ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ በተለያዩ የክስ መዝገቦች በሙስና ወንጀል በዐቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተበት ሜጀር ጄኔራል ክንፈ ዳኘው በነጻ ተለቋል በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፆ መዛግብቶቹ ገና በክርክር ሂደት ላይ የሚገኙ እና የተከሳሽን መከላከያ ምስክር ለመስማት የተቀጠሩ መሆናቸውን አረጋግጧል፡፡

የክሱን ሂደት የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስቴር በቀጣይ የሚገልጽ መሆኑን ማሳወቁን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.