የሀገር ውስጥ ዜና

በሽብርተኛው ቡድን ወረራ የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ቀያቸው የመመለሱ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል-የአማራ ክልል አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን

By Feven Bishaw

March 07, 2022

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 28 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሽብርተኛው ቡድን ወረራ የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ቀያቸው የመመለሱ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የአማራ ክልል አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር እያሱ መስፍን ገልጸዋል፡፡

በአሸባሪው ሸኔ ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ ወገኖችም በአብዛኛው በመጠለያ ጣቢያ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡