Fana: At a Speed of Life!

ስዊድን ለአፍሪካ የስነተዋልዶ ጤና አጠባበቅ ስትራቴጂ የሚውል ከ50 ሚሊየን ዶላር በላይ ድጋፍ አጸደቀች

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 29 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የስዊድን መንግስት ለአፍሪካ የስነተዋልዶ ጤና አጠባበቅ ስትራቴጂ የሚውል ከ50 ሚሊየን ዶላር በላይ ድጋፍ አጸደቀ።

የስዊድን መንግሥት በአፍሪካ ሀገራት ከፈረንጆቹ 2022 እስከ 2026 የሚያከናውነውን የስነተዋልዶ ጤና አጠባበቅና የጾታ ትንኮሳ መከላከልን የሚያግዝ አዲስ ስትራቴጂ ነድፏል።

በዚህም የሀገሪቱ መንግስት ለስትራቴጂው ተደራሽነትና በዘርፉ ለሚከናወኑት ስራዎች ተጨማሪ 500 ሚሊየን የስዊድን መገበያያ ገንዘብ ክሮና ወይም ከ50 ሚሊየን 735 ሺህ ዶላር በላይ ድጋፍ ማጽደቁ ተገልጿል።

አሁን የጸደቀው ድጋፍ የስዊድን መንግስት የሚያከናውናቸውን የሰብአዊ መብት ጥበቃ ተግባራትን እንደሚያግዝ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.