የሸገር ዳቦ ምርት ከነገ ጀምሮ ለገበያ መቅረብ ይጀምራል- ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ነገር ግን እነዚህ ምርቶች ዝቅተኛውንና በተለይም ቅድሚያ ወደሚሰጠው ህዝብ በሚፈለገው ደረጃ መድረስ ላይ እጥረቶች እንዳሉ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አንስተዋል፡፡
ይህንንም ለመቅረፍም የከተማ አስተዳደሩ የጀመረው ቁጥጥር ቢኖርም በተለይም የዳቦ በመንግስት ከፍተኛ ድጎማ እየቀረበ ሳለ የተሻለ ገቢ ያላቸው የንግድ ድርጅቶችና ባለሃብቶች ምርቱን ወስደው የሚያተርፉበት ሁኔታ እንዳለ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ህብረተሰቡ ይህንን ሁኔታ በመጠቆም፣ በማጋለጥ፣ በመቆጣጠር በኩል ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቀርበው ከተማው የንግዱ ማህበረሰብም በመተሳሰብ ለጊዜው ትርፍ ቀንሰው ህዝቡን እንዲያተርፉ ጠይቀዋል፡፡