Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ የፀሃይ ሃይል ፓርክን ማስፋፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 1 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ትዝታ ሙሉጌታ ከዓለም አቀፉ ታዳሽ የፀሃይ ኃይል ኅብረት ልዑካን ቡድን ጋር መከሩ፡፡

አምባሳደር ትዝታ ኅብረቱ በኢትዮጵያ ከሚፈጽመው ተልዕኮ ጋር በተገናኘ ከልዑካን ቡድኑ ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡

ታዳሽ የፀሃይ ኃይልን በኢትዮጵያ በመጠቀም ውሃ ለመግፋት እና የአገልግሎት ሥርዓቱን ለማሻሻል ብሎም ታዳሽ የፀሃይ ኃይል ፓርክ በኢትዮጵያ ማስፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.