የሀገር ውስጥ ዜና

የብፁዕ አቡነ መርቆሬዎስ አስከሬን የሽኝትና የቀብር ስነ-ስርዓት የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ

By Feven Bishaw

March 11, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አስከሬን ሽኝትና ለቀብር ስነ ስርዓት ዝግ የሚሆኑና ተለዋጭ መንገዶችን ይፋ ማድረጉን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

የሽኝቱና የቀብር ስነ-ስርዓቱ በሰላም እንዲከናወን የፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡