ዓለምአቀፋዊ ዜና

የግብፅ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

By Tibebu Kebede

February 25, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብፅ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሙባረክ በ91 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።

በፈረንጆቹ 2011 በህዝባዊ አመፅ ከስልጣን የተወገዱት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሀገሪቷን ለ30 ዓመታት መርተዋል።