አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከዚህ ቀደም በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው የነበሩ 63 ተጠርጣሪዎች ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ።
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ፀጋ እና የመስሪያ ቤቱ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ቱኑ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥተዋል።