አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የበልግ ወቅት በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሙቀት መጠን የሚመዘገብበት መሆኑንና አሁን እየተስተዋለ ያለው ነገር ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢኒስቲቲዩት ገለፀ፡፡
የኢኒስቲቲዩቱ የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አህመዲን አብዱልከሪም በበልግ ወቅት የዝናብ ተጠቃሚዎች መደበኛና ከመደበኛ በታች ዝናብ እንደሚኖርና በሙቀቱ ምክንያት በውሃ አካላትና ግድቦች ላይ ያለው የትነት መጠን እንደሚጨምር ገልፀዋል፡፡