Fana: At a Speed of Life!

አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ ከተመድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ ጉዳዮች የሥራ ሃላፊዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 12 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ሙሀመድ ዑመር ከተመድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ እርዳታ ሃላፊ ዶር ካትሪን ሱዚ የተመራ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልዑካን ቡድን ከክልሉ መንግስት ጋር በዘላቂ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ የሁለትዮሽ ስምምነት የተፈረመ ሲሆን፥ በክልሉ የተከሰተው ድርቅ በህብረተሰቡ ህይወት ላይ ካደረሰው ተፅዕኖ መልሶ ለማቋቋምና ዘላቂ የልማት መርሃ ግብሮችን ለመተግበር የሚያስችሉ ፕሮጀክቶችን በማቀድና በመተግበር ላይ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በመጨረሻም በክልሉ በተደጋጋሚ የሚከሰተውን ድርቅ ለመከላከል የአምስት ዓመታት የልማት ፕሮጀክቶች ስምምነት በመፈራረም ውይይቱ መጠናቀቁን የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.