የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ጣሊያን አቀኑ

By Tibebu Kebede

February 25, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ማምሻውን ወደ ጣሊያን አቅንተዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ በጣሊያን ቆይታቸው ከጣሊያኑ አቻቸው ጋር በሚኖራቸው ውይይት በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን የሁለትዮሽ ግንኙነትና ትብብር የበለጠ ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ።