የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ የንግዱ ዘርፍ ላይ ሙስና እና ብልሹ አሰራር እየተባባሰ መምጣቱ ተነገረ

By Feven Bishaw

March 21, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የንግዱ ዘርፍ ላይ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የፌደራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ገለጸ።

ኮሚሽኑ ”የንግድ ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ ማነቆ የወለደው ሙስና እና ብልሹ አሰራር” በሚል መሪ ሃሳብ ከተለያዩ የዘርፉ ተዋናዮች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡