የሀገር ውስጥ ዜና

በሀገር ውስጥ የዘይት አምራቾች ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ነው

By Feven Bishaw

March 22, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያዘጋጀው በሀገር ውስጥ የዘይት አምራቾች ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ያተኮረ ውይይት በመካሄድ ላይ ነው።

በውይይቱ የሀገር ውስጥ ዘይት አምራች ኩባንያዎችና ከዘይት ምርት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የመንግስት ተቋማት ተገኝተዋል።

 

ብዙ ጥያቄዎች የተነሱበት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በውይይቱ ተወካይ እንደሚልክ ቢያረጋግጥም ተወካዩ ከውይይቱ ቀርተዋል።