የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ በዋሽንግተን በሚካሄደው የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር እንደማትሳተፍ ገለፀች

By Tibebu Kebede

February 26, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ከሱዳን እና ግብጽ ጋር በአሜሪካ ሊካሄድ የታሰበው ድርድር ላይ እንደማትገኝ አስታወቀች።

የታላቁ የህዳሴ ግድብን የተመለከተ ውይይት በኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መካከል በአሜሪካ ግምጃ ቤት ሃላፊ እና የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት በታዛቢነት የተገኙበት የሶስትዮሽ ድርድር በአሜሪካ ሲካሄድ መቆየቱ ይታወሳል።