አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ከሱዳን እና ግብጽ ጋር በአሜሪካ ሊካሄድ የታሰበው ድርድር ላይ እንደማትገኝ አስታወቀች።
የታላቁ የህዳሴ ግድብን የተመለከተ ውይይት በኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን መካከል በአሜሪካ ግምጃ ቤት ሃላፊ እና የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት በታዛቢነት የተገኙበት የሶስትዮሽ ድርድር በአሜሪካ ሲካሄድ መቆየቱ ይታወሳል።