የሀገር ውስጥ ዜና

ሁሉንም የማሕበረሰብ ክፍል ቀርበን ልናዳምጠው ይገባል ያልነው ብዙ የሚነግረን ነገር እንዳለ ስለምናውቅ ነው – ከንቲባ አዳነች

By Feven Bishaw

March 23, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “ሁሉንም የማሕበረሰብ ክፍል ቀርበን ልናዳምጠው ይገባል ያልነው ብዙ የሚነግረን ነገር እንዳለ ስለምናውቅ ነው ” ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

በአዲስ አበባ ሲካሄድ በነበረው የህዝብ የውይይት መድረክ በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ከተሰብሳቢዎች የተነሱ ሲሆን÷ በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች የተሰጡትን አስተያቶች በሙሉ እንደ ግብዓት እንደሚወሰዱ አረጋግጠዋል፡፡