ዓለምአቀፋዊ ዜና

ሩስያ ህልውናዋ አደጋ ላይ የሚወድቅ ከሆነ የኑክሌር ጦር መሳሪያ ልትጠቀም ትችላለች – የክሬምሊን ቃል አቀባይ

By Feven Bishaw

March 23, 2022

አዲስ አበባ፣መጋቢት 14፣2014 (ኤፍ ቢሲ) ሩሲያ ህልውናዋ አደጋ ላይ የሚወድቅ ከሆነ የኑክሌር ጦር መሳሪያ ልትጠቀም እንደምትችል የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ተናገሩ፡፡

ቃል አቀባዩ ከመገናኛ ብዙሃን ጋር በነበራቸው ቆይታ፥ “ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ጦርነት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሊጠቀሙ ይችላሉ ወይ ?” የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት መልስ፥ ሩስያ የሀገር ውስጥ ደህንነት ፖሊሲ ያላት ሀገር መሆኗን ገልጸው ደህንነቷ አደጋ ላይ የሚወድቅ ከሆነ የኑክሌር ጦር መሳሪያ ጥቅም ላይ ልታውል ትችላለች ብለዋል፡፡