የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ ከሩሲያ ፌዴሬሽን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

March 25, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ ኢትዮጵያና ሩስያን የጋራ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ይበልጥ ተቀራርቦ ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ከሩሲያ ፌዴሬሽን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ከሆኑት ፒተር አሞሶቭ ጋር ተወያዩ።

በሩሲያ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር አለማየሁ ተገኑ ከሩስያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ፒተር አሞሶቭ ጋር ባካሄዱት ውይይት፥ ስለኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ከማስረዳታቸውም በተጨማሪ በኢንቨስትመንት፣ በንግድና ቱሪዝም ዘርፍ ያሉንን እምቅ ሃብቶች አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል።