የሀገር ውስጥ ዜና

ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት መስፈርቶችን በፖሊስ የስልጠና ስርዓት ትምህርት ማካተት በሚቻልበት ሁኔታ ውይይት ተካሄደ

By Tibebu Kebede

February 26, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት መስፈርቶች በፖሊስ የስልጠና ስርዓት ትምህርት ውስጥ በሚካተቱበት ሁኔታ ላይ ውይይት መካሄዱን ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ አስታወቀ።

በውይይቱ ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ እና ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የተውጣጡ ተወካዮች እንዲሁም የክልል ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋማት ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።