Fana: At a Speed of Life!

ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የምሥራቅ አፍሪካን ማኅበረሰብ ተቀላቀለች

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 20 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የምሥራቅ አፍሪካን ማኅበረሰብ ለመቀላቀል ያቀረበችው ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ ተገለጸ፡፡

ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የቀጠናው ሀገራት ዜጎች ያለገደብ በመንቀሳቀስ በሚያከናውኗቸው ነፃ የግብይት እና የንግድ ትሥሥር ተጠቃሚ ትሆናለች ተብሏል፡፡

የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረ-ሰብ ሊቀ መንበር እና የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በመሩት የበይነ-መረብ ጉባዔ ላይ ÷ “የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ወደ ቀጠናዊ ማኅበረሰቡ መቀላቀል በቀጠናዊ ውህደቱ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ክስተት ነው” ማለታቸውን የዘገበው ሲ ጂ ቲ ኤን ነው።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.