Fana: At a Speed of Life!

ክላረንስ ሴዶርፍ ከአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ጋር አዲስ አበባ ይመጣል

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የኔዘርላንድስ አማካይ ክላረንስ ሴዶርፍ ከአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ጋር አዲስ አበባ ይመጣል።

የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ሚያዚያ 2 ቀን ቅዳሜ በሸራተን አዲስ ከቀኑ 7 ሰአት ጀምሮ በሚካሄድ ስነ ስርአት በተመልካች ይጎበኛል።

ሴዶርፍም ከዋንጫው ጋር ሚያዚያ 2 ቀን ቅዳሜ በሸራተን አዲስ የሚገኝ ይሆናል።

ሴዶርፍ በተጫዋችነት ዘመኑ ከአያክስ፣ ሪያል ማድሪድ እና ኤሲ ሚላን ጋር ባለ ትልቁን ጆሮ ዋንጫ አራት ጊዜ አሸንፏል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.