የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ቡድን ወደ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ

By Alemayehu Geremew

April 01, 2022

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ቡድን ዳግም ወደ ፕሪሚየር ሊጉ መመለሱን አረጋገጠ።

በዛሬው የምድብ “ሐ” መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ቡድን ደቡብ ፖሊስን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያ መድን ከስምንት ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል።

ከዚህ ቀደም በምድብ “ሀ” የተደለደለው ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጉ ይታወሳል።