ቢዝነስ

ባለፉት ስምንት ወራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 52 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኘ

By Feven Bishaw

April 05, 2022

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 27 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ወራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 52 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአምስተኛ መደበኛ ጉባኤው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የስምንት ወራት እቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል።