አዲስ አበባ ፣ የካቲት 19 ፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን ሲያትም የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ።
ተጠርጣሪው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በተለምዶ ጨው በረንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከል ምክትል ዳይሬክተር ኮማንደር ታሪኩ መንገሻ ተናግረዋል።