በ18ኛ ሳምንት ፕሪሚየር ሊግ ሀዲያ ሆሳና ከአርባምንጭ ከተማ ጋር አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 3፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አስገራሚ ትዕይንት ያስተናገደው የሃዲያ ሆሳዕና እና አርባምንጭ ከተማ ጨዋታ 4 አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡
8 ጎሎች በተቆጠሩበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ አርባ ምንጭ ከተማ እስከ 80 ደቂቃ ሃዲያ ሆሳናን 4 ለ 1 ሲመራ ቢቆይም ነብሮቹ በ10 ደቂቃዎች ውስጥ በተከታታይ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል፡፡
ለአርባ ምንጭ ከተማ አህመድ ሁሴን 3 ጎሎችን በማስቆጠር ሃት – ትሪክ ሲሰራ ፀጋዬ አበራ ቀሪዋን አንድ ጎል ማስቆጠር ችሏል፡፡
ለሀዲያ ሆሳና ደግሞ ፍኖተየሱስ ተክለብርሃን፣ ሀብታሙ ታደሰ፣ ሄኖክ አፈወርቅ እና ብርሃኑ በቀለ ማስቆጠር ችለዋል፡፡