የሀገር ውስጥ ዜና

የፌደራልና የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች ጉባዔ በሰመራ እየተካሄደ ነው

By Tibebu Kebede

February 28, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 10ኛው የፌደራልና የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች ጉባዔ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በጉባዔው ላይ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ እና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል እንደሻው ጣሰውን ጨምሮ የሁሉም ክልሎች ፖሊስ ኮሚሽነሮች ተሳትፈዋል።