የሀገር ውስጥ ዜና

የአውሮፓ ህብረት ለቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ታዛቢዎችን እንደሚልክ ገለፀ

By Tibebu Kebede

February 28, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታካሂደው ሀገራዊ ምርጫ ታዛቢዎችን እንደሚልክ ገለፀ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይና የፀጥታ ፖሊሲ ኃላፊ እና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ቦሬል ፎንተልስ ጋር ተወያይተዋል።