የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በቤተመንግስት የኢፍጣር መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

By Meseret Awoke

April 16, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በታላቁ ቤተመንግስት የኢፍጣር ፕሮግራም እየተካሄደ ነው።

በታላቁ ቤተመንግስት እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ ግብር ላይ የእስልምና ኃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።

በዚህም የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ፣ የምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዚደንት ዶክተር ጀይላኒ ከድር ጨምሮ ታላላቅ አባቶች፣ ኢማሞች እና የእምነቱ ተከታዮች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!