ዓለምአቀፋዊ ዜና

በደቡብ አፍሪካ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ440 በላይ ደረሰ

By Feven Bishaw

April 18, 2022

ከአዲስ አበባ፣ሚያዚያ 10፣2014 (ኤፍ ቢሲ) ከጥቂት ቀናት በፊት በደቡብ አፍሪካ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 443 መድረሱ ተገለጸ፡፡

በደቡብ አፍሪካ ክዋዙሉ-ናታል ግዛት ከጥቂት ቀናት በፊት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የተከሰተውን የጎርፍ እና የአፈር መደርመስ አደጋን ተከትሎ ሁለት የፖሊስ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችን ጨምሮ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 443 የደረሰ ሲሆን በአደጋው ምክንያት እስካሁን የጠፉ 63 ሰዎችም እየተፈለጉ ነው ተብሏል፡፡