አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ13 ሺህ በላይ በሆኑ ኢንተርፕራይዞች በተለያዩ የገበያ ልማት መርኃ ግብሮች በመሳተፍ ከ5 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፍጠራቸውን የሥራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ገለጸ።
የሥራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ያዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር በዛሬው ዕለት በጦር ኃይሎች አደባባይ በይፋ ተከፍቷል።