ቢዝነስ

በ9 ወራት ከ3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች ተይዘዋል-ኮሚሽኑ

By Feven Bishaw

April 18, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉምሩክ ኮሚሽን በዘጠኝ ወራት ባደረገው ክትትል ከ3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፎች መያዛቸውን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ በ9 ወራት ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመቀናጀት ኮንትሮባንድን በመከላከል እና በመቆጣጠር ረገድ ያከናወናቸውን ሥራዎች በሚመለከት በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት አድርጓል።