በተደጋጋሚ ለሚነሱ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ ለመስጠት ያስችላል የተባለ ስምምነት ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የቻይናው ቴቢያን ኤሌክትሪክ አፓራተስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በተደጋጋሚ ለሚነሱ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ ለመስጠት እንደሚያችል የታመነበት የጂ አይ ኤስ ስዊች ጊር የማዕቀፍ ግዢ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱ ለተቋሙም ከፍተኛ የሆነ የጥገና ጊዜንና ወጪን በመቀነስ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ዕድል ይሰጣል ተብሏል።