የሀገር ውስጥ ዜና

በሆስፒታሉ ከ1 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የነጻ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና እየተሰጠ ነው

By Feven Bishaw

April 19, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከ1 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የነጻ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ።

የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ተመስገን ተሾመ ÷ ሆስፒታሉ ህክምናውን እየሰጠ ያለው ከ”ሂማሊያን ካታራክትና ላይፍ ፎር ዘ ዎርልድ” ከተሰኙ ግብረሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር መሆኑን ተናግረዋል።