በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሃድያ ሆሳዕና ድል ቀንቶታል
በአዲስ አበባ፣ሚያዝያ 11፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ19ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሀድያ ሆሳዕና አዳማ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ሀድያ ሆሳዕና ኦሞድ ኡኩሪ ከረጅም ጊዜ በኋላ ባስቆጠራት ጎል እስከ ዕረፍት 1 ለ 0 መምራት ችሏል፡፡
ከዕረፍት መልስ አዳማ ከተማ በአሜ ሙሀመድ ጎል አቻ መሆን ቢችልም ራምኬ ሎክ በ 87ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል ነብሮቹ ወሳኝ 3 ነጥብ ማግኘት ችለዋል፡፡
ሀድያ ሆሳዕና ዛሬ ማሸነፉን ተከትሎ በ 25 ነጥብ 4 ደረጃዎችን በማሻሻል ለጊዜው 7ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!