አዲስ አበባ ፣ የካቲት 21 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በቅርቡ ከኔዘርላንድስ የተመለሰው የ18ኛው ክፍለ ዘመን ዘውድ በትግራይ ክልል ለሚገኘው ጨለቆት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን ተመላሽ እንዲሆን ርክክብ ተደረገ::
በርክክቡ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳውን ፣የፌዴራልና የትግራይ ክልል ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች እና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።