አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በቤጂንግ በሚገኘውና በቻይና ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጣሪ በሆነው ሴንተር ፎር ቻይና ኤንድ ግሎባላይዜሽን (Center for China and Globalization ) ተገኝተው ለተቋሙ መስራችና ፕሬዚዳንት ዶክተር ሁዪኦ ዋንግ እና በተቋሙ ለሚገኙ ምሁራን በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አምባሳደሩ በማብራሪያቸው በኢትዮጵያ የሰሜኑ ክፍል የተከሰተው ጦርነት መንግስት ተገዶ የገባበት መሆኑንና ከጅማሮው አንስቶ ጦርነቱን ለማስቀረት ከፍተኛና ተደጋጋሚ ጥረቶችን አድርጎ እንደነበር አስታውሰዋል።