አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የትንሳዔና የኢድ-አልፈጥር በዓላት መቃረባቸውን ተከትሎ ሊኖር የሚችለውን የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ ችግር ለመፍታት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡
ተቋሙ በበዓላቱ ዋዜማና ዕለት የኤሌክትሪክ ኃይል ሳይቆራረጥና ሳይዋዥቅ ለማቅረብ አስቀድሞ የቅድመ መከላከል ሥራዎች እየተሰራ ሲሆን፥ ችግሩ ከተከሰተ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል የአስቸኳይ ጥገና ግብረ-ሃይል አዋቅሮ ወደ ስራ ገብቷል፡፡