የሀገር ውስጥ ዜና

በተለያዩ ከተሞች ለግብይት ሊውሉ የነበሩ ከ84 ሺህ በላይ ሀሰተኛ የብር ኖቶች ተያዙ

By ዮሐንስ ደርበው

April 21, 2022

በሌላ በኩል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሀሰተኛ  የብር ኖት በማዘዋወር የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች  በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

አንደኛው ተጠርጣሪ ወደ ባንክ በመሄድ ወደ አካውንቱ 3 ሺህ 500  ብር ገቢ ሲያደርግ÷ ከዚህ ውስጥ 1 ሺህ ሀሰተኛ ብር ቀላቅሎ አስገብቷል በሚል በባንኩ ሠራተኞች ጥርጣሬ ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል፡፡

በተመሳሳይ የሸቀጣ ሸቀጥ ሱቅ ባለቤት የሆነ ግለሰብ÷ ወደ ሱቁ እቃ ሊገዘ የመጣን ግለሰብ 3 ሺህ 400 ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ከዚህ በፊት የሰጠኸኝ አንተ ነህ በማለት በተፈጠረ አለመግባባት ፖሊስ በቦታው ደርሶ ሲያጣራ ሆን ብሎ ግለሰቡን ለመወንጀል አስቦ ያደረገው መሆኑ በመረጋገጡ በቁጥጥር ስር መዋሉን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡