አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 14፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሀገር ቤት” ጥሪን ተከትሎ ከተለያዩ የዓለም አገራት እንግዶች ወደ አገር ቤት እየገቡ መሆናቸው ተገለፀ፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ያቀረቡትን “ከኢድ እስከ ኢድ ወደ ሀገር ቤት” ጥሪ ተቀብለው የመጡ እንግዶች ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በቀረበው ጥሪ መሰረት ኢድን በጋራ እያከበርን፣ የተቸገሩ ወገኖችን በመጠየቅና በማገዝ ጥሩ ቆይታ ልናደርግ መጥተናል ብለዋል፡፡