የሀገር ውስጥ ዜና

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ለ837 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

By Feven Bishaw

April 22, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ837 ህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ ተክሌ በዛብህ ÷ የይቅርታ ሂደቱ በወንጀል ሕጉ ላይ የተቀመጠውን የይቅርታ አዋጅ መርህ ተከትሎ የተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡