የሀገር ውስጥ ዜና

በሀረሪ ክልል የሸዋል ኢድ በዓል አከባበር በተሳካ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑ ተገለፀ

By Feven Bishaw

April 22, 2022

አዲስ አበባ፣ሚያዚያ 14፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀረሪ ክልል የሸዋል ኢድ በዓል አከባበር በህዝቦች እና በሃይማኖቶች መካከል ፍቅርን፣ መቻቻልንና አብሮነትን ሊያጠናክር በሚችል መልኩ ለማክበር እየተሰራ መሆኑን የ የክልሉ ርዕሰ መስተደድር አቶ ኦርዲን በድሪ ተናገሩ፡፡

የሀረሪ ክልል ካቢኔ በክልሉ በተለይም ከሸዋል ኢድ በዓል ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ገምግሟል።