የሀገር ውስጥ ዜና

ሠመራ ዩኒቨርሲቲ እና የቱርኩ ማዐሪፍ ፋውንዴሽን በጋራ ለመስራት ተስማሙ

By Feven Bishaw

April 22, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሠመራ ዩኒቨርሲቲ ከቱርክ ማዐሪፍ ፋውንዴሽን ጋር በጋራ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራት ላይ ትኩረቱን ያደረገ የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር መሀመድ ኡስማን እና በኢትዮጵያ የቱርክ ማዐሪፍ ፋውንዴሽን ተወካይ ሌቬንት ሳሂን ተፈራርመዋል።