የሀገር ውስጥ ዜና

አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን በአግባቡ መጠቀም የጠነከረች ኢትዮጵያን የመገንባት እድል ነው – ምሁራን

By Feven Bishaw

April 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን በአግባቡ መጠቀም ከቻልን ከምንጊዜም በላይ የጠነከረች ኢትዮጵያን የምንገነባበት እድል ነው ሲሉ ምሁራን ተናገሩ፡፡

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ ረዳት ፕሮፌሰር አንዳርጋቸው ተስፋሁን÷ አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን ማቋቋም ብቻ ሳይሆን ዋናው ስራው ነው ውጤት የሚያመጣው ይላሉ።