አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖችን ከዕለት ድጋፍ ወደ መልሶ ማቋቋም ለማሸጋገር እየተሰራ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።
የክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ታረቀኝ ታሲሳ ÷ በክልሉ ሶስት ዞኖች እና አንድ ልዩ ወረዳ ተከስቶ በነበረው ችግር የተፈናቀሉ ወገኖች በመተከል ዞን እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡