የሀገር ውስጥ ዜና

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተፈናቃይ ወገኖችን ከዕለት ድጋፍ ወደ መልሶ ማቋቋም ለማሸጋገር እየተሰራ ነው

By Feven Bishaw

April 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖችን ከዕለት ድጋፍ ወደ መልሶ ማቋቋም ለማሸጋገር እየተሰራ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

የክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ታረቀኝ ታሲሳ ÷ በክልሉ ሶስት ዞኖች እና አንድ ልዩ ወረዳ ተከስቶ በነበረው ችግር የተፈናቀሉ ወገኖች በመተከል ዞን እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡